Skip to main content
image news

በሀዋሳ ከተማ አስተዳደር በ3 ወራት ውስጥ የተከናወኑ ዋና ዋና ተግባራት አፈፃፀም ሪፖርት የሲዳማ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ደስታ ሌዳሞ እና ካቢኒያቸው በተገኘበት እየተገመገመ ይገኛል።

የውይይት መድረኩን የመሩት የሲዳማ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ደስታ ሌዳሞ እንደገለጹት የሀዋሳ ከተማ ለነዋሪዎች የምትመች እና ሁለንተናዊ ብልፅግናዋ የተረጋገጠ እንድትሆን የተሻለ የአሰራር ስርዓት ተዘርግቶ በልዩ ትኩረት እየተመራ እንደሚገኝ አንስተዋል ።

የህዝብን አንገብጋቢ ጥያቄዎች ለመመለስ በሚያስችል መልኩ የከተማውን አመራር እንደ አዲስ በማደራጀት በርካታ ተግባራት ላይ ውጤት እያመጣ እንደሚገኝ ርዕሰ መስተዳድሩ በማንሳት ለከተማው ሁለንተናዊ ዕድገት እና ልማት አመራሩ በጊዜ የለኝም መንፈስ እንዲንቀሳቀስ መልዕክት አስተላልፈዋል።